“ትንሿ አገር” ብሎ ነው ኤርትራ ስልታዊ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደሚፈጸምባት የኤርትራ የተባበሩት መንግሥታት ልዩ የሰብዓዊ መብት ተከታታይ ራፖርተር ሞሐመድ አብደልሰላም ባቢከር ሰኞ በጄኔቫ በተካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ያስታውቁት። በኤርትራ የአፋር ተወላጆች የጄኖሳይድ ጥቃት፣ የማንነት መገፈፍ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው ማስታወቃቸው ይታወሳል።
3.5 የሚጠጋ ህዝብ እንዳላት አመልክተው በቅጽል ስሟ “ሰሜን ኮሪያ” በመባል የምታወቀው ኤርትራ ውስጥ የሚፈጸመው ስልታዊ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ በአጣዳፊ ሁኔታ ተጠያቂነትን የሚነሳባቸው ሊሆን እንደሚገባ ሪፖርቱ ጠቅሷል።
“The small country of around 3.5 million people in the Horn of Africa is sometimes nicknamed the North Korea of Africa” በማለት ኤርትራ ላይ የቀርበው ሪፖርት በኤርትራ የሚካሄዱት የሰብአዊ መብተት ጥሰቶች “ስልታዊ ናቸው” ማለቱ ከቀይ ባህር አፋሮች ንቅናቄ መሪ ማመልከቻ ጋር የሚገናኝ ሆኗል።
“ኤርትራ ከፕሬዚዳንት ኢሳያ በሁዋላ እንዴት ትመራ” በሚል አጀንዳ የኤርትራ መነግስት ተቃዋሚዎች በአሜሪካ ስብሰባ ሲያደረጉ በዋናነት ያነሱት በተለይም በአፋር ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ነበር። በወቅቱ የጀርመን ድምጽ የስብሰባውን አዘጋጅ ጠቅሶ “በደንከሊያ (አፋር) ሕዝብ ላይ የሚደርሰዉን ግፍና በደል በመሸሸሽ የሚፈናቀለዉና የሚሰደደዉ ሕዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል። ከ200 ሺሕ የሚበልጥ የኤርትራ አፋር ሕዝብ ወደ ኢትዮጵያ፣ጀቡቲና ወደ ሌሎች አካባቢዎች ተሰድደዋል።” ብሎ ነበር።
ከወራት በፊት ደግሞ በአዲስ አበባ ስብሰባ አድርጎ የነበረው የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ በኤርትራ የፖለቲካ፣ የደኅንነት፣ የኢኮኖሚ እና ሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ መነጋገሩን አስታውሶ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
የቀይ ባሕር አፋር ሕዝብ በተለየ ሁኔታ ከፍተኛ “መገለል እና በደል እየደረሰበት ነው” ያለው ድርጅቱ፣ ይህንኑ በደሉንና ተፈጸመ ያለውን ግፍ ዘርዝሮ ለተባበሩት መንግስታት ማቅረቡን አመልክቶም ነበር። ያለፉት ስድስት ዓመታት በትግል ሂደቱ የገጠሙት ፈታኝ ወቅቶች መሆናቸውን አስታውሶ፣ “አፋኝ” ያለውን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አገዛዝ በተባበረ ጥረት ማስወገድ የሚል አቋም መያዙን የድርጅቱ የውጭ ጉዳይ ግንኙነት ምክትል ኃላፊ እና የሊቀመንበሩ አማካሪ አቶ ነስረዲን አሕመድ ለዶቼ ቬለ መግለጻቸው አይዘነጋም።
መሪያቸውም በአልጀዚራ አማካይነት ባሰራጩት ተደጋጋሚ መረጃና ክስ ሲቀርበለት እንደነበረ በተደጋጋሚ ሲዘገብ ቆይቶ አሁን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ተከታታይ ሪፖርት እንዳለው፣ ለሦስት አስር ዓመታት ያለ ምርጫና ህግመንግስት ኤርትራን እየገዙ ያሉት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሚገዟት አገር ሕዝብ ላይ ከፍተኛ የመብት ጥሰት እንደሚፈጸሙ ይፋ አድርጓል።
ኤርትራ በተከታታይ ዓመታት በዓለም ላይ ካሉ አገራት በንጽጽር በሰብዓዊ መብቶች አያያዝና ጥበቃ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ተገልጿል። በፕሬስ ነጻነት ረገድ ከዓለም ሁሉ በመጨረሻ ናት።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ2022 ባወጣው የሰብዓዊ ልማት ደረጃ ኤርትራ ከ183 አገራት መካከል 175ኛ ሆና መመዝገቧን ቢቢሲ አማርኛ አስታውሷል።
ኢሳያስ ተቃውሞን በኃይል በማፈን፣ ተቃዋሚዎችን ያለፍርድ በማሰር እና በአስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ለብዙ ዓሥርተ ዓመታት በማቆየት ይከሰሳሉ። በታሰሩበት የጠፉ፣ የተረሸኑ፣ በግፍ ተሰቃይተው የደረሱበትን ቤተሰብ ሳያውቅ፣ እርም እንኳን ማውጣት የማይቻልባት አገር ኤርትራ በዚህ አካሄዷ አሁን አሁን ስሟ በከፍተኛ ደረጃ እየተነሳ ነው።
የመንግሥታቱ ድርጅት የኤርትራን ብሔራዊ አገልግሎት ሥርዓት ኤርትራውያንን ለዕድሜ ልክ ውትድርና ወይም ለግዳጅ ሥራ የሚዳረግ መሆኑን በመጥቀስ ከባርነት ጋር አመሳስሎታል። ይህንኑ ፍርሃቻ የኢርትራ አምራች ኃይል አገሩን ጥሎ መሰደዱ፣ ለስደት ሲወጡ በየበረሃውና ባህር ላይ ሕይወታቸው እንዳለፈ በተደጋጋሚ በአሳዛኝ ዜና የሚዘገብ ነው።
ወደ ኤርትራ እንዳይገቡ የተከለከሉት ባቢከር ያለ ምንም ክስ ወይም ፍርድ ለዓስርት ዓመታት ታስረው ስላሉበት ሁኔታ ምንም ተሰምቶ የማያውቁ ሰዎች ስማችውን መዘርዘር እንደሚቻል ጠቅሰው ነው የኢሳያስን አገዛዝ የወቀሱት።
በተባባበሩት መንግሥታት የኤርትራ ተወካይ ሐብቶም ዘርዓይ ሪፖርቱን “ግልጽነትና ሚዛናዊነት የጎደለው” ሲሉ አልተቀበሉትም።
ልበኤርትራ ላይ ለምክር ቤቱ ያቀረበው ልዩ ራፖርተር እንደ ካሁን ቀደሙ ሁሉ ባልተረጋገጡ መረጃዎች እና ማንነታቸው ባልታወቁ ምንጮች ላይ የተመሠረተ፣ ግልጽነትና ሚዛናዊነት የጎደለው፣ እንደሆነ ጠቅሰው ወኪሉ ሪፖርቱን ተቃውመዋል።
ኤርትራ ለረዥም ለዓመታት በሰብአዊ መብት ጥሰትና በግልጽ በሚታወቁ ወንጀሎች በአሜሪካ፣ አውሮፓና በተለያዩ አገራትና ተቋማት ያለማሳለስ ስትተች መቆየቷ አይዘነጋም።