የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የክልሉን ብሎም የሀገራችን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ተቀዳሚ ተግባሩን ለመወጣት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ተቋሙ የህዝብ የሰላምና ደህንነት ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚያስችል መልኩ የመዋቅርና የሰው ሀይል ስምሪት ማስተካከያዎችን ከማድረጉም በላይ ለአሰራር ያስቸግሩ የነበሩ ነባር ደንብና መመሪያዎችን አሻሽሏል እያሻሻለም ይገኛል፡፡
ከመሰረቱ የአማራ ህዝብን እንደ ጠላት ቆጥሮ መዋቅራዊ ጭቆናና ግፍ ሲያደርስ የነበረው አሸባሪው የህውሃት ቡድን ከአራት ኪሎ ከተባረረ ጀምሮ በግልፅና በስውር በክልላችንናበህዝባችን ሲያደርስ የነበረው ያልተቋረጠ ግፍ ወደ ለየለት ግልፅ ማጥቃት ሲሸጋገር ተቋሙ ለጊዜው የሚመጥን ዝግጅት በማድረግ ተገቢውን አመራር ሰጥቶ ጥቃቱን በሚገባ መክቷል፡፡አሸባሪው ቡድን ሀገርን ክዶና ደፍሮ በማዋረድ የተላለፈውን ቀይ መስመር ከሌሎች የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመቀናጀት መክቶ የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
ከዚህም ባሻገር ህብረተሰቡን ያሳተፈ የወንጀል መከላከል ስራዎችን በሁሉም አካባቢዎች ተግባራዊ በማድረግ በአንፃራነት የተረጋጋ ክልል ለመፍጠር እየተሰራ ነው፡፡የለውጥ ስራ ሂደት በአንድ ጀንበር የሚቋጭ አይሆንም እና ገና ህዝባችን ያላረካንና የአገልግለት አሰጣጥ ጉድለቶች ያሉብን ስለሆነ ከህዝባችን ጋራ በመሆን ወደ ፊት የተሻለአገልግሎት አሰጣጣችን እንዲኖር የለውጥ ስራውችን እየሰራን እንገኛለን፡፡
ይሁን እንጂ ክልሉን ለመወጠር ከውስጥ እስከ ውጭ ተናበው የሚሰሩ ሀይሎች የሚያደርሱት ተደጋጋሚ ጥፋት አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ከዚህ በፊት በሰሜን ሽዋ አጣየእና ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አካባቢ፤ በቅርቡም የቅማንት ፀንፈኛ ቡድን በተደራጀ መንገድ በጎንደር ከተማ ላይ አስቦት የነበረው ድርጊት የህዝባችን ሰላም ለማናጋት የክልሉን ሰላም የማደፍረስ ተልዕኮ አካል ነው ብለን እናምናለን፡፡
ዛሬም እንደ ትናንቱ የፀጥታ ሀይላችን ከህብረተሰቡ ጋር ተባብሮና ተቀናጅቶ የባንዳዎችን እኩይ ድርጊት የቀለበሰ ሲሆን በቀጣይ የድርጊቱ ተሳታፊዎች እና የደረሰውን ጉዳት ጥልቅ ምርመራ በማድረግ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ተቋማችን በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ለሰላም ወዳድ ህዝባችን ልናረጋገጥን እንወዳለን፡፡
የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራር ያለፉና የቀጣይ ሁኔታዎችን በመገምገም የቀጣይ የቀሪ ወራት ቁልፍ ተግባራትን ለይቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ ከክልል እስከ ቀበሌ ያሉ የተቋሙ አሰራሮችን በመፈተሸና ችግሮችን ለይቶ ለመደገፍ በተለይም 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ በክልላችን ያለምንን የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ የፖሊስ ሀይሉ ገለልተኝነት ያረጋገጥ ዕቅድና ስምሪት ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ለዚህም የመረጃና ደህንነት ስራዎችን በማጠናከር ከአጎራባች ክልሎች፣ ከፌዴራል የፀጥታ ተቋማት፣ ከብሄራዊ ደህንነት ጋር በትብብር እየተሰራ ሲሆን በአጠቃላይ በክልሉ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ በቅድመ መከላከል ላይ የተመሰረተ ፖሊሳዊ ተግባራትን ለመከወን በምናደርገው ጥረት ህብረተሰቡ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከጎናችን እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
በጀግንነት መጠበቅ በሰባዊነት ማገልገል
አማራ ፖሊስ ኮሚሽን ግንቦት 25/2013 ዓ.ም
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት።… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can Stop Cameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል