በቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል።
ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ ከቻይና ባለሀብቶች ጋር በመሆን እየገነቡት ያለው ይህ ፋብሪካ፤ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲገነቡ እቅድ ከተያዘላቸው ስድስት ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ እንደሆነ መገለጹ ይታወሳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ከቻይና ባለ ሀብቶች ጋር በመሆን ለመግንባት የያዛቸው ስድስቱ ፕሮጀክቶች፡-
- – በቀን 10ሺህ ቶን ሲሚቶ የሚያመርት ፋብሪካ
- – 30 ሚሊዮን ካሬ ሜትር ጂብሰም ቦርድ እና 400 ሺህ ቶን የዱቄት ጂብሰም በአመት የሚያመርት ፋብሪካ
- – በድሬዳዋ በቀን 3 ሺህ 500 ቶን ሲሚንቶ ለኤክስፖርት የሚያመርት ፋብሪካ
- – የድሬዳዋውን ነባር ፋብሪካ 30% የሚያሳድግ ፕሮጀክት
- – በአመት 350 ሺህ ቶን ብረት ማምረት የሚችል ፋብሪካ (በጥናት ላይ የሚገኝ)
- – ዳውሮ የድንጋይ ከሰል ማእድን ማውጫና ማጠብያ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ሚያዚያ 23 ቀን 2014 የግንባታው ጅምር በጎበኙበት ወቅት ስራው በአስራ አምስት ወር እንዲጠናቀቅና ባስቸኳይ ወደ ምርት እንዲገባ ልዩ ክትትል እንደሚደረግ በገለጹት መሰረት ነው ምረቃው በሚያዚያ እንደሚሆን ይፋ የሆነው።
በተያዘው ዕቅድ መሰረት ግንባታው በተጀመረ በአስራአንደኛው ወር ማለትም ዛሬ ፋብሪካው በቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ ለማምረት የሚያስችለውን የፕሪ ሂተር የመገጣጠሚያ ሥነ ሥርዓት ማከናወኑ ተመልክቷል።
ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግስ ግሩፕ ቦርድ ሊቀመንበር ዶክተር ብዙአየሁ ታደለ እንደተናገሩት፤ የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የክሊንከር ሲሚንቶ ማምረቻ የመጨረሻ ፍሎር የመገጣጠሚያ እና የሮተሪ መዝጊያ ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተካሄዷል።
የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ፕሮጀክት ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አበባው በቀል በበኩላቸው፤ በሀገሪቱ ውስጥ እያደገ ያለው የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ያጋጠመውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመፍታት እንዲቻል ፋብሪካው በቀን ከአስር ሺ ቶን በላይ ክሊንከር ማምረት የሚችል ነው ብለዋል።
ፋብሪካው በመጀመሪያው ዙር በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ ያመርታል ያሉት ኢንጂነር አበባው፤ የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ስኬታማ ከሚያደርጉ የግል ዘርፎች መካከል የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ ኢንደስትሪያል ኮምፕሌክስ አንዱ እንደሚሆን ታምኖበታልም ብለዋል።
በ18 ወራት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዟል። ፍብሪካው ወደ ስራ ሲገባ በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን እንደሚሸፍን ገልፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በ15 ወር እንዲጠናቅ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት እየተሰራ መሆኑን ኢንጂነር አበባው ጠቁመዋል።
ፋብሪካው ስራውን ሲጀምር ሲሚንቶ በመደበቅና እጥረት በመፍጠር ዋጋ እንዲንር ለሚያደርጉ መድሃኒት እንደሚሆንና አቅርቦቱን ሃምሳ ከመቶ የሚያሳድግ በመሆኑ ልዩ ትርጉም ያለው የዋጋ ቅናሽ እንደሚኖር ተጠቁሟል።
በአዲስ አበባ የመሬትና የቤት ዋጋ መቀነስ እይሳየ ባለበት በአሁኑ ወቅት ከብረት ዋጋ መቀነስ ጋር ተያይዞ የሲሚንቶ ችግር ከተቀረፈ ቅናሹ ይበልጥ እንደሚሆን ከወዲሁ እየተገመተ ነው። በከፍተኛ ዝርፊያ ላይ የተሰማሩ የሪል እስቴት ነጋዴዎች የዋናው ግብ አታቸው ሲሚንቶና ብረት ቅናሽ ሲታይ ዋጋቸውን እንዲያሻሽሉ ቁጥጥር እነደሚደረግ እየተሰማ ነው። የቤቶች ኮርፖሬሽን በጥራት ከፍ አድርጎ የሚገነባቸው ቤቶች በዋጋ ከግል ሪል እስቴቶች ጋር ሊመጣጠኑ እንደማይችሉ የሚጠቁሙ ዝርፎያው ሊገታ እንደሚገባ እየጠቆሙ ነው።
በዶላር እያሰሉ ክፚቸውን የሚያንሩት ሪል እስቴቶች ፣ ግብይታቸውን የሚያከናውኑት አገር ቤት በብር ነው። ግብይት የሚፈጽሙትም ከአገር ውስጥ አምራቾች ነው። ይህን የሚያነሱ እንደሚሉት የመንግስት ሚዲያዎችም ሆኑ “የዩቲዩብ ነጋዴዎች” ፊታቸውን ወደ እነዚህ ዘራፊዎች እንዲያዞሩ በርካቶች እይወተወቱ ነው።
- “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳየትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት… Read more: “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
- ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪምሰሞኑን ከሚሰማው የሐኪሞች የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎን ለጎን የተሰማው ዜና ሰፊ አድናቆት እየተቸረው ነው። ዶክተር ብሩክ ወይሻ ሙሽራነቱን አቋርጦ ነብስ ታድጓል፡፡… Read more: ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
- ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመበጦርነቱ ወቅት ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፕሮፌሰር ክንድያ ገብረህይወት “የደብረፅዮን ቡድን ከተደጋጋሚ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ነው” ሲሉ አጣጣሉት። ፋኖ አስራ ሶስት አመራሮችን… Read more: ፕሮፌሰር ክንድያ የደብረፅዮንን ቡድን “ካለፈ ስህተቱ የማይማር ተቸካይ ” አሉት፤ ፋኖ የደቦ አመራር ሰየመ
- The Wars We Still Can StopCameron Hudson (New York TimesMay Opinion Mr. Hudson is a senior fellow in the Africa program at the Center for Strategic… Read more: The Wars We Still Can Stop
- ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማልእየተንገዳግደ የፕሪማየር ሊጉን ዋናጫ ባያነሳም ኤፍ ኤ ካፕን ጨምሮ ሌሎች ዋንጫዎችን መውሰድ የቻለው ማንችስተር ዩናይትድ ለዩሮፕያን ሊግ ፍጻሜ ከቶትንሃም ጋር ደርሷል።… Read more: ዩናይትድ ለፍጻሜ አለፈ ቶተንሃምን ይገጥማል